VISITORS COUNTER


VISITORS COUNTER

Ticker

6/recent/ticker-posts

ስኖር ስኖር


                                                                       

ስኖር ስኖር የታገስኩት ይደክመኛል

ስኖር ስኖር የከዳኽኝ ቦታ ያመኛል

እሱን ሳልፈው የእናቴ እንባ ይፈጀኛል

ቀን ከለሊት እንዲህ ስትል ይሰማኛል

አንቺስ የቀየው ምሩቅ አድባሯ የታረቀችሽ

ለመካኗ ልጅ ሆነሻት አለቺኝ እሷ ያለችሽ

አይኑ ቢያዝ ምርኩዝ መሪ ለደካማው መደገፊያ

አለችን የምንልሽ ልጅ የሁላችን አይን ማረፊያ

ምነው ልጄ ከዚህ ብኩን ምኑ ጣለሽ

ምርቃትሽን በእርግማን ማን ቀየረሽ

ባፍረት አንገቴ ይደፋ እኔ እናትሽ አይን ይብላኝ

ብላ ደረቷን ስትደቃ ሳይ እንባዬን ውጬውም ከፋኝ  

ምከፋቴን ታውቀዋለህ 

መጎዳቴን ታየዋለህ

እኔ አንዷ ስንቱን ልቻል ስኖር ስኖር የታገስኩት ይደክመኛል

ስበረታ የከዳኻኝ ቦታ ያመኛል

እሱን ሳለፈው መጥፎ ሰዎች አፍገጠሙ ለአሉሽ አሉ

ጉድ ብለው ተዋደዱኝ ሰማህ ሰማሽ ተባባሉ

ስሜ መታረቂያቸው ሆነ ለተጣሉ በመንደሩ

ጨካኝ ክፉ ምህረት አልባ ለወደቀ የማይራሩ

እኔ አንዷ ስንቱን ልቻል ስኖር ስኖር የታገልኩት ይደክመኛል

አለህ ብዬ እያመንኩህ የከዳኸኝ ቦታ ያመኛል

ህመሜ ነህ አንተ ለኔ የልቤ ስርቻ ቁስል

የንፅህናዬ ጉደፍ የሃዘን ዘመኔ ምስል

አንተ ለኔ የእህህ ዜማ መልመጃዬ

ታሞ ታሞ ሲያገግሙ በግርሻ ስቃይ መክረሚያዬ

እኔ አንዷ ስንቱን ልቻል ልኖር የታገልኩት ይደክመኛል

እሱን ችዬም የከዳኸኝ ቦታ ያመኛል

እያረሩ መሳቅ ስማር እያቃሰቱ መፈገግ

ልቤን ደግሞ አደከመው መጨረሻህን መፈለግ

እኔ አንዷ ስንቱን ልቻል ልኖር የታገልኩት ይደክመኛል

እሱን ችዬም የከዳኸኝ ቦታ ያመኛል

                                                         20/10/2018

 

 

                                           ደራሲ እና ጋዜጠኛ ሜሮን መለሰ ሀብተወልድ

 

 

Post a Comment

0 Comments